ترجمة سورة الرحمن

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة الرحمن باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


አል-ረሕማን፤

ቁርኣንን አስተማረ፡፡

ሰውን ፈጠረ፡፡

መናገርን አስተማረው፡፡

ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡

ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡

ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡

በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡

መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡

ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡

በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡

የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡

ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡

የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡

ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡

በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›

ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?

በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
سورة الرحمن
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (الرَّحْمن) من السُّوَر المكية، وقد أبانت عن مقصدٍ عظيم؛ وهو إثباتُ عموم الرحمة لله عز وجل، وقد ذكَّر اللهُ عبادَه بنِعَمه وآلائه التي لا تُحصَى عليهم، وفي ذلك دعوةٌ لاتباع الإله الحقِّ المستحِق للعبودية، وقد اشتملت السورةُ الكريمة على آياتِ ترهيب وتخويف من عقاب الله، كما اشتملت على آياتٍ تُطمِع في رحمةِ الله ورضوانه وجِنانه.

ترتيبها المصحفي
55
نوعها
مكية
ألفاظها
352
ترتيب نزولها
97
العد المدني الأول
77
العد المدني الأخير
77
العد البصري
76
العد الكوفي
78
العد الشامي
78

* سورة (الرَّحْمن):

سُمِّيت سورة (الرَّحْمن) بهذا الاسم؛ لافتتاحها باسم (الرَّحْمن)، وهو اسمٌ من أسماءِ الله تعالى.

* ذكَرتْ سورةُ (الرحمن) كثيرًا من فضائلِ الله على عباده:

عن جابرِ بن عبدِ اللهِ رضي الله عنهما، قال: «خرَجَ رسولُ اللهِ ﷺ على أصحابِه، فقرَأَ عليهم سورةَ الرَّحْمنِ، مِن أوَّلِها إلى آخِرِها، فسكَتوا، فقال: «لقد قرَأْتُها على الجِنِّ ليلةَ الجِنِّ فكانوا أحسَنَ مردودًا منكم! كنتُ كلَّما أتَيْتُ على قولِه: {فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ}، قالوا: لا بشيءٍ مِن نِعَمِك رَبَّنا نُكذِّبُ؛ فلك الحمدُ!»». أخرجه الترمذي (٣٢٩١).

1. من نِعَم الله الظاهرة (١-١٣).

2. نعمة الخَلْق (١٤-١٦).

3. نِعَم الله في الآفاق (١٧-٢٥).

4. من لطائف النِّعَم (٢٦-٣٢).

5. تحدٍّ وإعجاز (٣٣-٣٦).

6. عاقبة المجرمين (٣٧-٤٥).

7. نعيم المتقين (٤٦-٧٨).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (7 /550).

مقصدُ سورة (الرَّحْمن) هو إثباتُ الرحمةِ العامة لله عز وجل، الظاهرةِ في إنعامه على خَلْقه، وأعظمُ هذه النِّعَم هو نزول القرآن، وما تبع ذلك من نِعَم كبيرة في هذا الكون.

يقول الزَّمَخْشريُّ: «عدَّد اللهُ عز وعلا آلاءه، فأراد أن يُقدِّم أولَ شيءٍ ما هو أسبَقُ قِدْمًا من ضروب آلائه وأصناف نَعْمائه؛ وهي نعمة الدِّين، فقدَّم من نعمة الدِّين ما هو في أعلى مراتبِها وأقصى مَراقيها؛ وهو إنعامُه بالقرآن وتنزيلُه وتعليمه؛ لأنه أعظَمُ وحيِ الله رتبةً، وأعلاه منزلةً، وأحسنه في أبواب الدِّين أثرًا، وهو سَنامُ الكتب السماوية ومِصْداقها والعِيارُ عليها.

وأخَّر ذِكْرَ خَلْقِ الإنسان عن ذكرِه، ثم أتبعه إياه؛ ليعلمَ أنه إنما خلَقه للدِّين، وليحيطَ علمًا بوحيِه وكتبِه وما خُلِق الإنسان من أجله، وكأنَّ الغرض في إنشائه كان مقدَّمًا عليه وسابقًا له، ثم ذكَر ما تميَّز به من سائر الحيوان من البيان؛ وهو المنطقُ الفصيح المُعرِب عما في الضمير». "الكشاف" للزمخشري (4 /443).