ترجمة سورة المرسلات

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني سورة المرسلات باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية.
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
سورة المرسلات
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (المُرسَلات) من السُّوَر المكية، نزلت بعد سورة (الهُمَزة)، وقد جاءت ببيانِ قدرة الله على بعثِ الناس بعد هلاكهم؛ فهو المتصفُ بالرُّبوبية والألوهية، وقد افتُتحت بمَشاهدِ القيامة، والتذكير بمَصارعِ الغابرين، وذكَرتْ تأمُّلات في خَلْقِ الإنسان والكون؛ ليعودَ الخلقُ إلى أوامرِ الله، وليستجيبوا له سبحانه، و(المُرسَلات): هي الرِّياحُ التي تهُبُّ متتابِعةً.

ترتيبها المصحفي
77
نوعها
مكية
ألفاظها
181
ترتيب نزولها
33
العد المدني الأول
50
العد المدني الأخير
50
العد البصري
50
العد الكوفي
50
العد الشامي
50

* سورة (المُرسَلات):

سُمِّيت سورة (المُرسَلات) بذلك؛ لافتتاحها بالقَسَمِ الإلهيِّ بـ(المُرسَلات)؛ وهي: الرِّياح التي تهُبُّ متتابِعةً.

سورة (المُرسَلات) من السُّوَر التي شيَّبتْ رسولَ الله صلى الله عليه وسلم:

عن ابنِ عباسٍ رضي الله عنهما، قال: «قال أبو بكرٍ الصِّدِّيقُ رضي الله عنه لرسولِ اللهِ صلى الله عليه وسلم: يا رسولَ اللهِ، أراكَ قد شِبْتَ! قال: «شيَّبتْني هُودٌ، والواقعةُ، والمُرسَلاتُ، و{عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ}، و{إِذَا اْلشَّمْسُ كُوِّرَتْ}». أخرجه الحاكم (3314).

1. مَشاهد القيامة (١-١٥).

2. مَصارع الغابرين (١٦-١٩).

3. تأمُّلات في خَلْقِ الإنسان والكون (٢٠-٢٨).

4. عودٌ لمَشاهد القيامة (٢٩-٥٠).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (8 /540).

مقصدُ سورة (المُرسَلات): الاستدلالُ على وقوع البعث بعد فَناء الدنيا، والاستدلال على إمكانِ إعادة الخَلْقِ بما سبَق من خَلْقِ الإنسان وخلق الأرض، وفي ذلك دلائلُ على قدرة الله، واتصافِه بالوَحْدانية والرُّبوبية.

ينظر: "التحرير والتنوير" لابن عاشور (29 /419).