ترجمة سورة النجم

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة النجم باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡

ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡

ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡

ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡

(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡

ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡

እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡

ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡

እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡

ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡

(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡

ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡

ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡

መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡

እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡

እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡

ያለበሳትንም አለበሳት፡፡

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?

ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡

ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡

ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡

ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?

ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?

እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡

ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡
سورة النجم
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (النَّجْم) من السُّوَر المكية، نزلت بعد سورة (الإخلاص)، وقد أشارت إلى صدقِ النبيِّ صلى الله عليه وسلم في تبليغه الرسالةَ، ونفيِ الهوى عنه، وأن كلَّ ما جاء به هو وحيٌ من عند الله، عن طريق جبريلَ عليه السلام؛ فحاشاه صلى الله عليه وسلم أن يفتريَ على الله الكذبَ، كما جاءت السورةُ الكريمة بإثبات بطلان الآلهة التي يَدْعُونها من دُونِ الله؛ فهو وحده المستحِقُّ للعبادة.

ترتيبها المصحفي
53
نوعها
مكية
ألفاظها
361
ترتيب نزولها
23
العد المدني الأول
61
العد المدني الأخير
61
العد البصري
61
العد الكوفي
62
العد الشامي
61

*  سورة (النَّجْم):

سُمِّيت سورة (النَّجْم) بهذا الاسم؛ لافتتاحها بقَسَم الله عز وجل بالنَّجْم.

* سورة (النَّجْم) هي أولُ سورةٍ أُنزلت فيها سجدةٌ:

عن عبدِ اللهِ بن مسعودٍ رضي الله عنه، قال: «أولُ سورةٍ أُنزِلتْ فيها سَجْدةٌ: {وَاْلنَّجْمِ}، قال: فسجَدَ رسولُ اللهِ ﷺ، وسجَدَ مَن خَلْفَه، إلا رجُلًا رأَيْتُه أخَذَ كفًّا مِن ترابٍ فسجَدَ عليه، فرأَيْتُه بعدَ ذلك قُتِلَ كافرًا؛ وهو أُمَيَّةُ بنُ خَلَفٍ». أخرجه البخاري (٤٨٦٣).

1. إثبات الوحيِ، وتزكيةُ مَن أُنزِلَ عليه (١-١٨).

2. الظنُّ لا يغني من الحق شيئًا (١٩-٣٢).

3. ذمُّ المشركين، وبيانُ وَحْدة رسالة التوحيد (٣٣- ٦٢).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (7 /490).

مقصدُ السورة الأعظم هو إثبات صدقِ النبي صلى الله عليه وسلم فيما جاء به، ونفيِ الهوى عنه، فلا يَتكلَّم إلا بما علَّمه اللهُ إياه عن طريق الوحيِ؛ فهو الصادقُ المصدوق المبعوث من عند القويِّ المتعال، وفي ذلك يقول ابنُ عاشور رحمه الله مشيرًا إلى مقصودها: «تحقيقُ أن الرسول صلى الله عليه وسلم صادقٌ فيما يبلغه عن الله تعالى، وأنه مُنزَّه عما ادَّعَوْهُ.

وإثباتُ أن القرآن وحيٌ من عند الله بواسطة جبريل.

وتقريبُ صفة نزول جبريل بالوحيِ في حالينِ؛ زيادةً في تقرير أنه وحيٌ من الله واقع لا محالةَ.

وإبطالُ إلهيَّة أصنام المشركين.

وإبطال قولهم في اللاتِ والعُزَّى ومَناةَ: بناتُ الله، وأنها أوهام لا حقائقَ لها، وتنظيرُ قولهم فيها بقولهم في الملائكة: إنهم إناثٌ». "التحرير والتنوير" لابن عاشور (27 /88).

وينظر: "مصاعد النظر للإشراف على مقاصد السور" للبقاعي (3 /35).