ترجمة سورة الليل

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة الليل باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡
سورة الليل
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (اللَّيل) مكية، نزلت بعد سورة (الأعلى)، وقد افتُتحت بقَسَم الله عز وجل بـ(اللَّيل)، وهو آيةٌ من آيات الله الدالةِ على عظمته وقُدْرته وتصرُّفه في هذا الكون، وبيَّنت السورة الكريمة تبايُنَ مَساعي البشر، المؤديَ إلى تبايُنِ مستقرَّاتهم في الدار الآخرة، وفي ذلك دعوةٌ إلى السعيِ إلى الخير، وتركِ الشر.

ترتيبها المصحفي
92
نوعها
مكية
ألفاظها
71
ترتيب نزولها
9
العد المدني الأول
21
العد المدني الأخير
21
العد البصري
21
العد الكوفي
21
العد الشامي
21

* سورة (اللَّيل):

سُمِّيت سورة (اللَّيل) بهذا الاسم؛ لافتتاحها بقَسَمِ الله عز وجل بـ(اللَّيل).

1. القَسَم على تبايُنِ سعي البشر (١-٤).

2. اعملوا فكلٌّ مُيسَّر (٥-١٣).

3. إنذار وتحذير (١٤- ٢١).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (9/172).

بيانُ قدرة الله عزَّ وجلَّ، وتصرُّفِه في هذا الكون، وتبايُنِ سعيِ البشر المؤدي إلى تباين مآلاتهم.

ينظر: "التحرير والتنوير" لابن عاشور (30 /378).