ترجمة سورة الفجر

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة الفجر باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


በጎህ እምላለሁ፡፡

በዐሥር ሌሊቶችም፡፡

በጥንዱም በነጠላውም፡፡

በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡

በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?

ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡

በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡

ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡

ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
سورة الفجر
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (الفجر) من السُّوَر المكية، نزلت بعد سورة (الليل)، وقد افتُتحت بقَسَمِ الله عز وجل بـ(الفجر)، وجاءت على ذكرِ ما عذَّب اللهُ به عادًا وثمودَ وقوم فرعون؛ ليعتبِرَ بذلك مشركو قريش، وفي ذلك تثبيتٌ للنبي صلى الله عليه وسلم على طريق الدعوة، وخُتمت السورة الكريمة بتقسيم الناس إلى أهل الشقاء وأهل السعادة.

ترتيبها المصحفي
89
نوعها
مكية
ألفاظها
139
ترتيب نزولها
10
العد المدني الأول
32
العد المدني الأخير
32
العد البصري
29
العد الكوفي
30
العد الشامي
30

* سورة (الفجر):

سُمِّيت سورة (الفجر) بهذا الاسم؛ لافتتاحها بقَسَمِ الله عز وجل بـ(الفجر)؛ قال تعالى: {وَاْلْفَجْرِ} [الفجر: 1].

1. في التاريخ عِبْرة وعِظة (١-١٤).

2. أهل الشقاء وأهل السعادة (١٥- ٣٠).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (9 /127).

مقصدُ السورة هو إنذارُ قُرَيش بعذاب الآخرة عن طريقِ ضربِ المثَلِ في إعراضهم عن قَبول رسالة ربهم بمثَلِ عادٍ وثمودَ وقومِ فرعون، وما أوقَعَ اللهُ بهم من عذاب، وفي ذلك تثبيتُ النبي صلى الله عليه وسلم على هذه الدعوة.

ينظر: "التحرير والتنوير" لابن عاشور (30 /312).