ترجمة سورة النازعات

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة النازعات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

የሙሳ ወሬ መጣልህን?

ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

የካደ ሰውማ፣

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
سورة النازعات
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (النَّازعات) من السُّوَر المكية، وقد افتُتحت بذكرِ الملائكة التي تَنزِع الأرواح؛ ليبعثَ اللهُ الناس بعد ذلك في يوم الطامَّة الكبرى؛ ليكونَ من اتقى في الجِنان، ويذهبَ من طغى وآثر الحياةَ الدنيا إلى الجحيم مأواه، وقد ذكَّرت السورةُ الكريمة بنِعَمِ الله على خَلْقه وقوَّته وقهره بعد أن بيَّنتْ إقامةَ الحُجَّة على الكافرين، كما أقام موسى عليه السلام الحُجَّةَ على فرعون بالإبلاغ.

ترتيبها المصحفي
79
نوعها
مكية
ألفاظها
179
ترتيب نزولها
81
العد المدني الأول
45
العد المدني الأخير
45
العد البصري
45
العد الكوفي
46
العد الشامي
45

- قوله تعالى: {يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ اْلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَىٰهَا ٤٢ فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَىٰهَآ} [النازعات: 42-43]:

عن عائشةَ رضي الله عنها، قالت: «كان النبيُّ صلى الله عليه وسلم يُسألُ عن الساعةِ حتى أُنزِلَ عليه: {يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ اْلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَىٰهَا ٤٢ فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَىٰهَآ} [النازعات: 42-43]». أخرجه الحاكم (3895).

* سورة (النَّازعات):

سُمِّيت سورة (النَّازعات) بذلك؛ لافتتاحها بقَسَمِ الله بـ(النَّازعات)؛ وهم: الملائكةُ الذين ينتزعون أرواحَ بني آدم.

1. مَشاهد اليوم الآخِر (١-١٤).

2. قصة موسى عليه السلام مع فرعون (١٥-٢٦).

3. لفتُ النظر إلى خَلْقِ السموات والأرض (٢٧-٣٣).

4. أحداث يوم القيامة (٣٤-٤١).

5. سؤال المشركين عن وقتِ الساعة (٤٢-٤٦).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (9 /23).

يقول ابنُ عاشور رحمه الله: «اشتملت على إثباتِ البعث والجزاء، وإبطال إحالة المشركين وقوعَه، وتهويلِ يومه، وما يعتري الناسَ حينئذٍ من الوَهَلِ، وإبطال قول المشركين بتعذُّرِ الإحياء بعد انعدام الأجساد». "التحرير والتنوير" لابن عاشور (30 /59).