ترجمة سورة عبس

Sadiq and Sani - Amharic translation

ترجمة معاني سورة عبس باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation.


ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

የተብቃቃው ሰውማ፤

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

ከናቱም ካባቱም፤

ከሚስቱም ከልጁም፤

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
سورة عبس
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (عبَسَ) من السُّوَر المكية، وقد نزلت في عتابِ الله نبيَّه صلى الله عليه وسلم في إعراضه عن ابنِ أمِّ مكتومٍ الأعمى، بسبب انشغاله مع صناديدِ قريش، وهذا العتاب لتعليم النبي صلى الله عليه وسلم المقارنةَ بين المصالح والمفاسد، وإعلاءٌ من شأن النبي صلى الله عليه وسلم، كما جاءت السورة على ذكرِ آيات الله ونِعَمه على خَلْقِه؛ مذكِّرةً إياهم بيوم (الصاخَّة)، حين ينقسم الناس إلى أهل جِنان، وأهل نيران.

ترتيبها المصحفي
80
نوعها
مكية
ألفاظها
133
ترتيب نزولها
24
العد المدني الأول
42
العد المدني الأخير
42
العد البصري
41
العد الكوفي
42
العد الشامي
40

* قوله تعالى: {عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ ١ أَن جَآءَهُ اْلْأَعْمَىٰ ٢ وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ ٣ أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ اْلذِّكْرَىٰٓ} [عبس: 1-4]:

عن عُرْوةَ، عن عائشةَ أمِّ المؤمنين رضي الله عنها، قالت: «أُنزِلتْ في ابنِ أمِّ مكتومٍ الأعمى»، قالت: «أتى النبيَّ ﷺ، فجعَلَ يقولُ: يا نبيَّ اللهِ، أرشِدْني! قالت: وعند النبيِّ ﷺ رجُلٌ مِن عُظَماءِ المشركين، فجعَلَ النبيُّ ﷺ يُعرِضُ عنه، ويُقبِلُ على الآخَرِ، فقال النبيُّ ﷺ: «يا فلانُ، أتَرى بما أقولُ بأسًا؟»، فيقولُ: لا؛ فنزَلتْ: {عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ} [عبس: 1]». أخرجه ابن حبان (٥٣٥).

* سورة (عبَسَ):

سُمِّيت سورة (عبَسَ) بذلك؛ لقوله تعالى في أولها: {عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ} [عبس: 1].

1. عتابُ المُحبِّ (١-١٦).

2. تفكُّر وتدبُّر (١٧-٣٢).
3. يومَك.. يومَك (٣٣-٤٢).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (9 /41).

عتابُ اللهِ نبيَّه صلى الله عليه وسلم عتابَ المُحبِّ؛ لتزكيةِ نفس النبي صلى الله عليه وسلم، ولتعليمه الموازنةَ بين مراتبِ المصالح والمفاسد، وفي حادثةِ عُبُوسِه صلى الله عليه وسلم في وجهِ الأعمى أوضَحُ الدلالة على ذلك.

ينظر: "مصاعد النظر للإشراف على مقاصد السور" للبقاعي (3 /157)، "التحرير والتنوير" لابن عاشور (30 /102).