ترجمة سورة الواقعة

الترجمة الأمهرية

ترجمة معاني سورة الواقعة باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية.
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
የምትዘሩትንም አያችሁን?
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
سورة الواقعة
معلومات السورة
الكتب
الفتاوى
الأقوال
التفسيرات

سورة (الواقعة) من السُّوَر المكية، نزلت بعد سورة (طه)، وقد جاءت بتذكيرِ الناس بوقوع يوم القيامة؛ للدَّلالة على عظمة الله عز وجل، وترهيبًا لهم من مخالفة أوامره، ودعوةً لهم إلى اتباع الدِّين الحق وتركِ الباطل، وخُتمت السورة الكريمة بتعظيمِ القرآن، وصدقِ أخباره وما جاء به، وقد أُثر عن النبي صلى الله عليه وسلم قراءتُه لها في صلاة الفجر.

ترتيبها المصحفي
56
نوعها
مكية
ألفاظها
380
ترتيب نزولها
46
العد المدني الأول
99
العد المدني الأخير
99
العد البصري
97
العد الكوفي
96
العد الشامي
99

* قوله تعالى: {فَلَآ أُقْسِمُ بِمَوَٰقِعِ اْلنُّجُومِ ٧٥ وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوْ تَعْلَمُونَ عَظِيمٌ ٧٦ إِنَّهُۥ لَقُرْءَانٞ كَرِيمٞ ٧٧ فِي كِتَٰبٖ مَّكْنُونٖ ٧٨ لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا اْلْمُطَهَّرُونَ ٧٩ تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ اْلْعَٰلَمِينَ ٨٠ أَفَبِهَٰذَا اْلْحَدِيثِ أَنتُم مُّدْهِنُونَ ٨١ وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ} [الواقعة: 75-82]:

عن عبدِ اللهِ بن عباسٍ رضي الله عنهما، قال: «مُطِرَ الناسُ على عهدِ النبيِّ ﷺ، فقال النبيُّ ﷺ: «أصبَحَ مِن الناسِ شاكرٌ، ومنهم كافرٌ، قالوا: هذه رحمةُ اللهِ، وقال بعضُهم: لقد صدَقَ نَوْءُ كذا وكذا»، قال: فنزَلتْ هذه الآيةُ: {فَلَآ أُقْسِمُ بِمَوَٰقِعِ اْلنُّجُومِ} [الواقعة: 75]، حتى بلَغَ: {وَتَجْعَلُونَ رِزْقَكُمْ أَنَّكُمْ تُكَذِّبُونَ} [الواقعة: 82]». أخرجه مسلم (٧٣).

* سورة (الواقعة):

سُمِّيت هذه السورة بـ(الواقعة)؛ لافتتاحِها بهذا اللفظ، ولتسميةِ النبيِّ صلى الله عليه وسلم لها بذلك:

عن أبي بكرٍ الصِّدِّيقِ رضي الله عنه، قال: «سألتُ رسولَ اللهِ ﷺ: ما شيَّبَكَ؟ قال: «سورةُ هودٍ، والواقعةِ، و{عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ}، و{إِذَا اْلشَّمْسُ كُوِّرَتْ}»». أخرجه الترمذي (٣٢٩٧).

و(الواقعةُ): اسمٌ من أسماءِ يوم القيامة.

* سورة (الواقعة) من السُّوَر التي شيَّبتْ رسولَ الله صلى الله عليه وسلم:

عن أبي بكرٍ الصِّدِّيقِ رضي الله عنه، قال: «سألتُ رسولَ اللهِ ﷺ: ما شيَّبَكَ؟ قال: «سورةُ هودٍ، والواقعةِ، و{عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ}، و{إِذَا اْلشَّمْسُ كُوِّرَتْ}»». أخرجه الترمذي (٣٢٩٧).

* أُثِر عن النبي صلى الله عليه وسلم قراءتُه لسورة (الواقعة) في صلاة الفجر:

عن جابرِ بن سَمُرةَ رضي الله عنه، قال: «كان رسولُ اللهِ ﷺ يُصلِّي الصَّلواتِ كنَحْوٍ مِن صلاتِكم التي تُصَلُّون اليومَ، ولكنَّه كان يُخفِّفُ، كانت صَلاتُه أخَفَّ مِن صَلاتِكم، وكان يَقرأُ في الفجرِ الواقعةَ، ونحوَها مِن السُّوَرِ». أخرجه أحمد (٢٠٩٩٥).

1. تحقيق القيامة (١-٥٦).

2. دلائلُ البعث والجزاء (٥٧-٧٤).

3. تعظيم القرآن، وصدقُ أخباره (٧٥-٩٦).

ينظر: "التفسير الموضوعي لسور القرآن الكريم" لمجموعة من العلماء (7 /598).

مقصدُ سورة (الواقعة) هو التذكيرُ بوقوع يوم القيامة وهَوْلِه، ووصفُ ما يحدُثُ به؛ لتخويف الناس وترهيبهم من معصية الله عز وجل ومخالفة أمره، وفي ذلك دعوةٌ لهم للرجوع إلى الحق، والاستجابة لأمر الله.

ويُبيِّن ابن عاشور محورَها فيقول: «هو التذكيرُ بيوم القيامة، وتحقيق وقوعه.

ووصفُ ما يَعرِض لهذا العالَمِ الأرضي عند ساعة القيامة.

ثم صفة أهل الجنة وبعض نعيمهم.

وصفة أهل النار وما هم فيه من العذاب، وأن ذلك لتكذيبهم بالبعث.

وإثبات الحشر والجزاء.

والاستدلال على إمكان الخَلْق الثاني بما أبدعه الله من الموجودات بعد أن لم تكن.

والاستدلال بدلائل قدرة الله تعالى.

والاستدلال بنزعِ الله الأرواحَ من الأجساد والناس كارهون لا يستطيع أحدٌ مَنْعَها من الخروج، على أن الذي قدَرَ على نزعها بدون مُدافعٍ قادرٌ على إرجاعها متى أراد على أن يُمِيتَهم.

وتأكيد أن القرآن منزلٌ من عند الله، وأنه نعمةٌ أنعم الله بها عليهم فلم يشكروها، وكذَّبوا بما فيه». "التحرير والتنوير" لابن عاشور (27 /280).